Archive by Author

የኢኮኖሚ ዕድገቱ ሲፈተሽ

በቅርቡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህኅበር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዓመታዊውን አለም አቀፍ ኮንፈረንስ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ስብሰባው ከሌሎች አመታት በተሻለ በጥራትም ሆነ በብዛት ወረቀቶች የቀረቡበት በመሆኑ የሚደነቅ ነበር፡፡…ጥናቶቹ እንደሚያሳዩት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ከዓመት ዓመት እየቀነሰ ነው፡፡ ገበሬው የተሻሻሉ የምርት ግብዓቶችን የመጠቀም ፍላጎቱም እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከግብርና ልማት ሠራተኞች ጋር ያለው ትብብርም አመርቂ አይደለም፡፡ እውነታው እንዲህ ከሆነ፣ ጥያቄው፣ “በየቀኑ የሚደሰኮርልን ተስፈንጣሪ የምርት ዕድገት ከየት መጣ?” ነው፡፡

Read more
www.helping-education-ethiopia.orgschools.html

የትምህርት ነገር

በ2000 ዓ.ም. የመግቢያ ፈተናውን ያለፉት ተማሪዎች 22.2 በመቶ ቢሆኑም ዩኒቨርሲቲ የገቡት ግን 88.1 በመቶ ናቸው፡፡ በሌላ አነጋገር 65.9 በመቶ የሚሆኑት ወዳቂ ተማሪዎች አለአግባብ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተደልድለዋል፡፡ ስለሆነም በዚህ ዓመት ከገቡት ተማሪዎች መካከል ሁለት ሶስተኛው ዩኒቨርሲቲ መግባት የማይገባቸው ነበሩ ማለት ነው፡፡ ከቀሪው አንድ ሦስትኛ መካከልም አብዛኛው ፈተናውን እንደነገሩ ያለፈ /ከ50 እስከ 60 በማግኘት/ ተማሪ ነው፡፡ በመግቢያ ፈተናው ከ60 በመቶ በላይ ያመጡት “እንቁ” ተማሪዎቻችን /ድንቄም እንቁ!/ 8.2 ከመቶ ብቻ ከሆኑ ተማሪ ቤቶቻችንን ለምን ወደ ሌላ ትርፋማ የስራ ዘርፍ አይዛወሩም?

Read more

የምርጫ ትንበያ

እስካሁን ካየሁት በመነሳት ባለኝ ግምት በአዲስ አበባ ኢህአዴግ 2/3ኛውን ወንበር ያሸንፋል፡፡ በክልሎች፡ ምናልባት በአማራ፣ መኢአድ 20 በመቶ፣ መድረክ /በከተሞች/ 10 በመቶ፣ ኤዴፓ 5 በመቶ ያገኙ ይሆናል፡፡ ቀሪውን ግን ኢህአዴግ የሚያሸንፍ ይመስለኛል፡፡ በኦሮሚያ እንዲሁ መድረክ ምናልባት 15 በመቶ ያገኝ ይሆናል፡፡ በትግራይ አረና ከ7 እስከ 10 መቀመጫዎች ሳያሸንፍ አይቀርም፡፡ በደቡብ መድረክ 10 በመቶ፣ መኢአድ 10 በመቶ፣ ኢዴፓ 5 በመቶ ያገኙ ይሆናል፡፡ በሌሎቹ ክልሎች ተቃዋሚዎች ብዙ ተወዳዳሪ ያቀረቡ ስላልመሰለኝ ምናልባት ሁለት ወይ ሶስት ወንበሮች ያገኙ ይሆናል፡፡ ቀሪዎቹ፣ እነ መኢብን፣ቅንጅት፣ መኢዴፓ፣ኢሰዴፓ፣ ኢፍዴኃግ ወዘተ አንድም ወንበር ያገኛሉ ብዬ አልጠብቅም፡፡

Read more

“ኤርትራን ያስገነጠልነው ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” የአቶ መለስ አዲስ ግኝት

አቶ መለስ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ህወሓት ከሻዕቢያ ጋር ለምን እንደወገነ ሲመልሱ “ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” ብለውናል፡፡ ይህ መቼም በጣም የሚያስገርም ግኝት ሳይሆን አልቀረም፡፡ አቶ መለስ አሳምረው እንደሚያውቁት፣ አቦይ ስብሐትም በቅርቡ ሲናገሩ እንደተደመጡት፣ ህወሓት የኤርትራ ጥያቄ “የቅኝ ግዛት ጥያቄ” መሆኑን ተቀብሎ ለኤርትራ ነጻነት ሲታገል የነበረ ድርጅት ነው፡፡ እንዲያውም የኤርትራን ነጻነት ከራሱ ከሻዕቢያ ሳይቀር የታደገ መሆኑን አቦይ ስብሐት በግልጽ አረጋግጠዋል፡፡ ይህ ዓላማ ኢትዮጵያን ከመበታተን ከማዳን ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም፡፡ ሲጀመር ስሙ እንደሚያመለክተው ህወሓት ትግራይን /እና ኤርትራን/ ነጻ ለማውጣት የተቋቋመ ድርጅት እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት ጉዳይ ጉዳዩ የነበረ/የሆነ ድርጅት አልነበረም፡፡ ስለሆነም ህወሓት ትብብሩን የሚያራምደው “የትግራይን ሕዝብ” መብት ከማስጠበቅ አንጻር እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት አስጨንቆት አልነበረም፡፡ …ሙሉውን ለማነበብ የድረ ገጹን የአማርኛ ክፍል ይጎብኙ።

Read more

“ኤርትራን ያስገነጠልነው ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” የአቶ መለስ አዲስ ግኝት

አቶ መለስ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ህወሓት ከሻዕቢያ ጋር ለምን እንደወገነ ሲመልሱ “ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” ብለውናል፡፡ ይህ መቼም በጣም የሚያስገርም ግኝት ሳይሆን አልቀረም፡፡ አቶ መለስ አሳምረው እንደሚያውቁት፣ አቦይ ስብሐትም በቅርቡ ሲናገሩ እንደተደመጡት፣ ህወሓት የኤርትራ ጥያቄ “የቅኝ ግዛት ጥያቄ” መሆኑን ተቀብሎ ለኤርትራ ነጻነት ሲታገል የነበረ ድርጅት ነው፡፡ እንዲያውም የኤርትራን ነጻነት ከራሱ ከሻዕቢያ ሳይቀር የታደገ መሆኑን አቦይ ስብሐት በግልጽ አረጋግጠዋል፡፡ ይህ ዓላማ ኢትዮጵያን ከመበታተን ከማዳን ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም፡፡ ሲጀመር ስሙ እንደሚያመለክተው ህወሓት ትግራይን /እና ኤርትራን/ ነጻ ለማውጣት የተቋቋመ ድርጅት እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት ጉዳይ ጉዳዩ የነበረ/የሆነ ድርጅት አልነበረም፡፡ ስለሆነም ህወሓት ትብብሩን የሚያራምደው “የትግራይን ሕዝብ” መብት ከማስጠበቅ አንጻር እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት አስጨንቆት አልነበረም፡፡

Read more