Archive | Religion/Life/Education RSS feed for this section
ከአዲግራት እስከ ዛላንበሳ፤ ቁርጥራጭ ማስታወሻዎች (ክፍል አንድ)

ከአዲግራት እስከ ዛላንበሳ፤ ቁርጥራጭ ማስታወሻዎች (ክፍል አንድ)

‘ለአዲሳባ “ሸገር” የሚል የዳቦ ስም ከሰጠን ለአዲግራት ምን እንላለን?’ የሚል የሚኒስትሪ ፈተና ጥያቄ ቢመጣ ስንት ተማሪ እንደሚመልሰው አላውቅም። “ወልዋሎ” ካሉ መልሱን አግኝተውታል፡፡ ይህ ስም በከተማዋ ሁሉም ነገር ላይ ተፅፎ ይታያል፡፡ “ወልዋሎ ፀጉር ቤት”፣”ወልዋሎ እንዳ-ባኒ” (ዳቦ ቤት ማለት ነው)፣ “ወልዋሎ ሙዚቃ ቤት”፣ “ወልዋሎ ጥህሎ ቤት”… “ወልዋሎ ከረንቡላ”…የወልዋሎ ነገር ማቆምያ የለውም፡፡ ከ ወልዋሎ የተረፉት አገልግሎት መስጫዎች ደግሞ “አግኣዚ” በሚል ነው የሚጠሩት፡፡ “አግአዚ” በአዲግራት ከተማ ከትምህርት ቤት እስከ ቡና ቤት ያለ ማንኛውም ድርጅት ሊጠራበት የሚችል ስም ነው፡፡ አግአዚ ቡቲክ፣አግአዚ ኢንተርኔት፣ አግኣዚ ትምህርት ቤት፣አግአዚ መሸታ ቤት…ወዘተ
በከተማዋ የሚገኘው ቁጥር አንድ የምሽት ክለብ “ፍሪ -ዞን” ይባላል፡፡ ለመዲናችን አዲስ አበባ እንኳ የሚመጥን ዘመናዊ ክለብ ነበር፡፡ ሆኖም ክለቡ ከከተማዋ በብዙ እርምጃ በመቅደሙ በገበያ እጦት ተዘግቷል፡፡ የዛሬን አያድርገውና አዲግራት የሞቀች-ያበደች፣ አሸሼ ገዳሜ የሚባልባት ከተማ ነበረች አሉ፡፡ የድንበር ጦርነት ጉሮሮዋን ዘጋው፡፡ ብዙዎቹ ነዋሪዎቿም ተሰደዱ፣ ወደ መቀሌ፣ወደ አዲሳባ፡፡

Read more
n51658023525_1517284_8889

Ababa Tesfaye to Host New Show

The well-liked and honored children’s program host, Tesfaye Sahilu – known as “Ababa Tesfaye” – is hosting a new show to be shown at Panoramic Theater, the new theater in the Martyr’s building.
* * *
From Our Archive: Ababa Tesfaye’s Great Journey (Interview)

A couple of months before we started Addis Neger newspaper, the same team launched a website called Ethiomirror. It was a short-lived project. Most of the articles were read only by a very small number of people. Here we publish an Interview with the great Ababa Tesfaye. He had been the background sound for Ethiopian children for the past forty years. Fired from his work, he makes a living by selling his books.

Read more

የኤደን ፣ የቤቲ እና የሜላት አማርኛ

ለግል ት/ቤቶች የፈረንጅ ምስል የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ በጉልህ የሚታየው የደሞዝ ልዩነትም ለዚህ ጥሩ ማስረጃ ነው፡፡ አንድ በግል ት/ቤት የሚገኝ ምንም አይነት ዲፕሎማም ሆነ ዲግሪ የሌለው ፈረንጅ የቆዳ ቀለሙ ነጭ በመሆኑ ብቻ ማስተርስ ካለው ኢትዮጵያዊ በአምስት እጥፍ የበለጠ ደሞዝ ያገኛል፡፡ የአንድ ፈረንጅ አማካይ ደሞዝ ከ 5-11 ሺ የኢትዮጵያ ብር ይደርሳል፡፡ በአንጻሩ ሁለተኛ ዲግሪና ረዥም የስራ ልምድ ያለው ኢትየጵያዊ መምህር 3 ሺ ብር የክፍያ ጣርያው ነው፡፡

በእነዚህ ትምህርት ቤቶች ከፈረንጆች ቀጥሎ ጥሩ ክፍያ የሚያገኙት ህንዶች፣ ጃማይካዎችና ሌሎች የአፍሪካ ዜግነት ያላቸው መምህራን ናቸው፡፡ ሆኖም በስደት ወደ ሶስተኛ አገር ለመሄድ አዲስ አበባ የሚኖሩ አፍሪካውያን በ‹‹ሀበሻ›› ደሞዝ ሊቀጠሩ ይችላሉ፡፡

Read more

ዲቪ እና CV

ነገሩ ስላስደነቀኝ ተጨማሪ ነገር ለማግኘት በዩኒቨርስቲው ግቢ መዘዋወር ጀመርኩ፡፡ የዲቪ ማስታወቂያዎች በተማሪዎች ካፌ፣ በመማርያ ክፍሎች ደጅ ባሉ የማስታወቂያ ሰሌዳዎች፣ በቤተ መጻሕፍቱ በር ላይ ወዘተ ተለጣጥፎ አየሁ፡፡ የማስታወቂያው ይዘት ተማሪዎች ዕድሉ እንዳያመልጣቸው እና እንዲጠቀሙበት የሚያባብል ነው፡፡ የተማሪዎች ካውንስል ነው ይህንን የሚስተባብረው፡፡ በኔ ጊዜ የነበረው የተማሪዎች ካውንስል የመንግሥት ለውጥ እንዲመጣ ያስተባብር እንደነበር ትዝ አለኝ፡፡

Read more

ጓሳ – ያልተዘመረለት ተፈጥሮ

(በመሀመድ ሰልማን) …አቶ መለስ “መሀል ሜዳ” የመጡ ጊዜ ታድያ ሰውየው ያረፉበት ስፍራ “ሕይወት ሆቴል” በሚባል አነስተኛ የገጠር መዝናኛ መሆኑ ተነግሮኝ ይህንኑ ለማረጋገጥ ሄድኩኝ፡፡ ሆቴሏ በከተማዋ መሀል ትገኛለች፡፡ ሙሉ በሙሉ የጭቃ ቤት ስትሆን ጥግ ጥጉን የተሰሩ ወደ ጎን ያዘመሙ መኝታ ክፍሎችና አንድ ምግብ ቤት በውስጧ ይዛለች፡፡ የሆቴሉ እመቤት የሀበሻ ቀሚስ አድርገው፣ ግዙፍ መነፅራቸውን ደቅነው ለምሳ ቤታቸው የተገኘውን ሰው ለማብላት ተፍ ተፍ ሲሉ አገኘኋቸው፡፡…

ደብረብርሃን፣ ባኬሎ፣ ጣርማ በር፣ መዘዞ፣ ማዞርያ፣ ጓሳ፣ መሀል ሜዳ፡፡ እነዚህ ወዳልተዘመረለት የጓሳ ምድር የሚያደርሱ የኢትዮጵያ ትንንሽ ከተሞች ናቸው፡፡ አዲስ አበባን መነሻ ካደረግን 260 ኪሎ ሜትር መራቅ ይኖርብናል፡፡ ይህ ድንቅ ስፍራ እንደ አክሱም ሽቅብ የተቀሰረ ሀውልት የለውም፤ እንደ ላሊበላ በፍልፍል ድንጋይ አልታነፀም፤ እንደ ኤርታሌ የሚንተከተክ ላቫ አልፈጠረበትም፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የተዘረጋ የፕላቶ ሸንተረር ነው፡፡ ግን ልብን ወከክ የሚያደርግ፣ ቢያዩት ቢያዩት የማይጠገብ እንዲሁም የማያልቅ፣ እንዲሁም የማይደክም ግን ደግሞ ሩቅና ሰ…ፊ!
ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ ወይም ወደ የአማርኛውን ክፍል ይጎብኙ።

Read more