የአገር ወይስ የሥነ ጽሑፍ ፍቅር?
ይስማእከ በመጽሐፉ መግቢያ ላይ የሚጠቅሳቸው እና “የሥነ ጽሑፍ ስብራቱን” በ “ወጌሻ ምክራቸው” እንደጠገኑለት የሚያወድሳቸው “መካሪዎቹ” ያላዩዋቸው የሚመስሉ እጅግ ብዙ፣ ብዙ “ስብራቶች” በመጽሐፉ ውስጥ በጉልህ ይስተዋላሉ። የይስማእከ በእድሜ ወጣት ከመኾኑ የተነሳ እንደ ባለቅኔው ጸጋዬ ገብረመድኅን አባባል “በሳርም፣ ባሳርም” ተምሮ ያልጨረሳቸው ብዙ ጉዳዮች ሊኖሩ እንደሚችሉ ግልጽ ነው። (በድፍረት የሠራቸው ብዙ ስህተቶች እንዳሉ ባይዘነጋም) በመጽሐፉ መግቢያ ላይ ስማቸውን ያነሳቸው የሥነ ጽሑፍ ባለሞያዎች ግን እነኚህን የሚጎረብጡ ስህተቶች እንዴት ሊያልፏቸው እንደቻሉ ለብዙዎች ያስገርማቸዋል። በእርግጥ ይስማእከ እነዚህ ሰዎች በመጽሐፉ ላይ የነበራቸው አስተዋጽዖ እስከምን ድረስ እንደነበረ አይነግረንም። በመኾኑም እነዚህን ሰዎች እርሱ ስማቸውን ስለጠቀሰ ብቻ የስህተቱ አጋር አድርጎ ማሰብም አስቸጋሪ ሊኾን ይችላል። ይስማእከም የእነርሱን አስተያየት “ሙሉ በሙሉ” እንዳልተቀበለ በስልክ ውይይታችን ላይ ገልጿል። ምክንያትም አለው፤ “የራሴ የኾኑ ቀለሞች ከመጽሐፉ እንዲጠፉ አልፈለግሁም” የሚል።
Read more
24 December 2010 