Archive by Author

የጠፋው ትውልድ [አንድ ለቅዳሜ]

“የጠፋው ትውልድ” የሽግግር ዘመኖች ትውልድ ነው፤ ለዚያውም የከሸፉ ሽግግሮች። ይህ ጠቃሚ ጎኖች ቢኖሩትም ጉዳቶችም አሉት። አንዱ ጉዳቱ ትውልዱ በፖለቲካው ውስጥ አሻራውን የሚተውበት እድልና ጊዜ ማጣቱ ነው። ሆኖም ይህ ትውልድ ደርግ እና ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ መኖር ያልነበረባቸው፣ ድጋሚም መምጣት የሌለባቸው የፖለቲካ ስርአቶችና አመራሮች መሆናቸውን ኖሮ አይቷቸዋል። ይህ ትውልድ ሁሉንም ፖለቲካዊ ጽንፎች በአያቶላዎቹ ሲተነተኑ ሰምቷል፤ በፊት አውራሪዎቹ ሲተገበሩ አይቷል፣ ኖሯቸዋልም። ይህ ትውልድ የፖለቲካ ሐላፊነቱን ካልተወጣ አገራችን አዳዲስ ደርጎች እና አዳዲስ ኢህአዴጎችን ማስተናገዷ እንደማይቀር እሰጋለሁ። ያን ጊዜ ብዙ መንግሥቱዎች ወይም ብዙ መለሶች ይወሩናል፤ አያርግብንና! “የጠፋው ትውልድ” ከዚህ ልምድ የሚቀስመው ትምህርት አገሪቱን ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲ የሚያሸጋገር ቀመር እና ፖለቲከኞች እንዲያፈራ ይረዳው ይሆን?
ይህ ትውልድ በመሠረቱ ስለ አገርም ይሁን ስለ ፖለቲካ ያለው አመለካከት በቅድሚያ የተቃኘው “እናት አገር” ወይም “ኢትዮጵያ” በሚለው ጽንሰ ሐሳብ ዙሪያ ነው። የ“እናት አገር” ገናና ታሪክ፣ ሉአላዊነት እና አንድነት የፖለቲካው እንብርት ነበር። ስለ እናት አገር ለተከታዩ “አዲሱ ትውልድ” የሚተርፍ አክብሮትና ፍቅር ያደረበትም ለዚህ ነው። የአክብሮቱና የፍቅሩ መገለጫ ሁሉ “ትክክል” መሆኑን ግን እጠራጠራለሁ። አብዛኛው በተለይም ከተማ ቀመሱ በ”እናት አገር” ርዕዮተ ዓለማዊና ባህላዊ መሠረት ቢቀረጽም፣ በሒደት “በብሔረሰብ መብት” አስተምህሮ መማረክ የጀመሩ ቁጥራቸው የማይናቅ የትውልዱ አባላት አሉ።

Read more
Politics “Genna” Version!

Politics “Genna” Version!

Part of the lesson that the EPRDF took from the 2005 election was how to deal with religiously- affiliated individuals and groups. Its increasing control over the leadership of religious institutions is one aspect of the measures taken. The most obtrusive tactic employed in the last five years is infiltrating every inch of seemingly independent space within religious institutions and groups – recruiting all religiously active individuals or convincing them to stay away from politics altogether.

Rreligion remains an important factor in our politics, whether politicians recognize it or not. We should not ignore or avoid religion all together for political, social and national interests. Religious institutions and affiliated groups can play a positive role in supporting democracy and development. They can provide a grassroots level platform for deliberation and exercise of democracy. By the same token, they can be used to suppress people, as Marxists rightly argued. ‘Genna’, the birth of Jesus Christ, is about hope. Can our religions give us any hope about our politics?

Read more

ይቅር ባይ፣ ይቅር ተባይ፣ ይቅር አባባይ አሉ? ይቅርታና እርቅስ?

አንድ ጥፋተኛ የተባለ ወይም የሆነ ሰው “ይቅርታ” “ጠይቆ” ከእስር ወይም ከሌላ ዓይነት ቅጣት “ነጻ” መደረጉን በራሱ የሚቃወም ሰው ብዙ አይገኝም። ቁም ነገሩ ያለው ይቅር ባዩ “ስለጥፋቱ” ወይም አጠፋ ስለተባለው ነገር የደረሰበት ልባዊ ድምዳሜ፤ ይቅርታውን የሚጠይቅበት ምክንያት እና ፋይዳው ብቻ አይደለም። ይቅርታ ተጠያቂው እና አድራጊውም ወገን ደረሰብኝ ስለሚለው ጉዳት ብቻ ሳይሆን ስለጉዳቱ አድራሽ፣ ይቅርታውን ስለሚሰጥበት የሞራል እና የሕግ መሠረት እንዲሁም ስለይቅርታው ተናጠላዊና ሁለንተናዊ ፋይዳ የሚኖረው እምነትና ግብ የይቅርታውን ምንነት በተጨባጭ ይወስነዋል። ብዙውን ጊዜ ደግሞ በሁለቱ መካከል ይቅር አባባዮች አሉ። የእነርሱ ማንነት፣ የሞራል ተቀባይነት፣ በተግባር ለሕሊናዊ ዳኝነት የሚሰጡት ቦታ እና ከእርቁ ውጤት የሚፈልጉት ነገርም እንዲሁ እርቁን እርቅ የሚያደርግ፤ አለዚያም ድራማ የሚያሰኝ ሊሆን ይችላል።

አንድ ነጥብ በድጋሚ ላስረግጥ፤ እነዚህ በሦስቱም ወገኖች ዘንድ ሊፈተኑ የሚገባቸው ነገሮች ተሟሉም አልተሟሉም እንዲሁ “በሰብአዊነት” ብቻ የታሰረ “ከተጸጸተና ይቅርታ ከጠየቀ” መፈታቱን መደገፍ ከእርቅና ከይቅርታ ጥልቅ ሞራላዊና ስነልቦናዊ ትርጉምና ውጤት ጋራ ተፈጥሯዊ ግንኙነት ላይኖረው ይችላል። እንዲህ ሲሆን ይቅርታ ጠያቂውም፣ ሰጪውም ሆነ አሸማጋዩ ወገን (አንዱ ወይም ሁሉም) ድራማ እየሠሩ እንኳን ቢሆን እነርሱ ብዙዎቻችን በተግባር የማናውቀውንና የማናደርገውን የይቅርታ መንፈስ ተጋሪዎች ሊሆኑ አይችሉም።

Read more

[አንድ ለቅዳሜ] ስለ ፖለቲከኞቻችን ምን ይነበባል? እነርሱስ ምን ያነባሉ?

ለመሆኑ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የመሪነት ሚና የመጫወት ፍላጎት ያለው ሰው እንዲያነባቸው የሚመከሩ መጻሕፍት የትኞቹ ናቸው? አንዳንድ ጊዜ የምንረዳበት መንገድና መጠን ቢለያይ እንኳን ስለ አገራችንም ይሁል ስለሌላ ስለሚጠቅመን ጉዳይ ተቀራራቢ መረጃ (ትርጉም አላልኩም) እንዲኖረን ሊነበቡ ይገባቸዋል የምንላቸው መጻሕፍት (ግምታዊ) ዝርዝር ቢኖረን የሚጠላ አይደለም። “የተሳሳቱ መረጃዎች የተሳሳተ ሕግ ይወልዳሉ” የሚባለው እንዳይደርስብን ፖለቲከኞቻችን ቢያውቁት፣ ቢገነዘቡት የምንላቸውን መሠረታዊ ጉዳዮች እንዲረዱልን ልናግዛቸው ይገባል፤ በአንድ በኩል ፖለቲከኞች የእኛው ስራ ውጤቶች ናቸውና።

ነገሩ ሰፊ ክርክር የማጫር እድል ቢኖረውም አንባብያን የአገራችን ፖለቲከኞች ሊያነቧቸው ይገባል ወይም ቢያነቧቸው ጥሩ ነው የምትሏቸውን መጻሕፍት ዝርዝር እንድታካፍሉኝ ልጋብዝ። በመጨረሻ የመጻሕፍቱን ዝርዝር እዚሁ መልሰን እናትማቸዋለን። መጻሕፍቱ በየትኛውም ቋንቋ የተጻፉ፤ ኢልቦለድም ልቦለድም ሊሆኑ ይችላሉ። ታሪክ፣ ፖለቲካ፣ የሕዝብ አስተዳደር፣ ኢኮኖሚ፣ ሕግ ወዘተ እያሉ ማሰቡ ያግዝ ይሆናል። የመጽሐፍ ርእስ ከጠፋ በርእሰ ጉዳይ ለምሳሌም “ሐሳብን ስለመግለጽ ነጻነት፤ ስለ ሕግ ልእልና ወዘተ ቢያነቡ” ብሎ ሐሳብ መስጠት አይከፋም።

Read more

[አንድ ለቅዳሜ] የአዲስ ርእዮተ ዓለማዊ ትንተና ጅማሮ

እዚህ ላይ “አማካይ” ርእዮተ ዓለማዊ አማራጫ መቅረብ/መገኘት እንዳለበት በተደጋጋሚ ይነገራል። ተገቢም ነው። እኔም ይህን እደግፋለሁ፤ ፖለቲካ በአንድ በኩል ሙከራ ስለሆነም ጭምር። ነገር ግን ሁሉም በአማካይ ፍለጋ ብቻ መጠመድ የለበትም፤ ምክንያቱም ትክክለኛው ወይም የተሻለው አማራጭ አማካዩ ላይሆን ይችላልና። ለዚህም ነው በሌኒናዊ ግራ አመለካከት ታፍኖ የቆየው ፖለቲካ በመሠረቱ የተለየ የሆነውን የቀኝ/ሊበራል አመለካከት ለማስተናገድ ረጅም ጊዜና ትግል ያልጠየቀው። ከትምህርት እና ከከተሜነት መስፋፋት ጋራ የሚወለዱ አዳዲስ ፍላጎቶች ተፈጥረዋል፣ ይፈጠራሉም። ስለዚህም እነርሱን ርእዮተ ዓለማዊ ቅርጽ እየሰጡ የሚተነትኑ አማራጮች ያስፈልጋሉ።

Read more