Archive by Author
Negaso_Gidada_Et_339025gm-a

ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ

የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ። የመጀመርያ የጡረታ አበላቸውን ትላንት ጥቅምት 17 ቀን 2003 ዓ.ም የተቀበሉት ዶክተር ነጋሶ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነታቸው ሊያገኙ የሚገባቸውን ሕጋዊ ጥቅማ ጥቅም እስከ አሁን ማግኘት እንዳልቻሉ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። በተከበረላቸው የጡረታ ገንዘብ ላይ አስተያየታቸውን ለአዲስ ነገር የሰጡት ዶክተር ነጋሶ “በዚህ የኑሮ ውድነት እንዴት ተደርጎ ነው በ1197 [...]

Read more
BulchaDemeksa2009_3

OFDM to Elect a New Chairperson

According to outgoing Chairperson Bulcha Demekssa, he is not the only leader to be replaced by the new leadership team. Bulcha says, “I am not the only leader to be replaced. The election is meant to replace all of the leadership team members.” Bulcha does not want to disclose the venue of the meeting, fearing interference from government cadres.

Read more

Breaking News: Free at Last! Birtukan Released from Jail

(UPDATE) Addis Neger Online has confirmed that the jailed opposition leader Birtukan Mideksa has been freed from  prison. -Birtukan said that she requested pardon from government. -Birtukan’s first interviewer was VOA’s Meleskachew Amaha. -Our correspondent in Addis Ababa said that he had never seen such an emotional welcome. -Birtukan walked on red carpet to get [...]

Read more

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ “ከእስር ሊለቀቁ ነው”

ላለፈው አንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት በእስር ላይ የቆዩት የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትሕ ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ማታ ወይም በነገው ዕለት እንደሚፈቱ የአዲስ ነገር ምንጮች ገለጹ። ሆኖም በምን ዐይነት ቅድመ ኹኔታ እንደሚፈቱ እንደማያውቁ ምንጮች ተናግረዋል።
እንደምንጮቹ ገለጻ ከሆነ ብርቱካንን የማስፈታት ሂደት የተጀመረው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአዲስ ዓመት የመጀመርያ ሳምንት ላይ የሀገር ሽማግሌዎችን “መጥታችሁ እንድፈታት ጠይቁ እና ትፈታ” የሚል መልእክት መላካቸውን ተከትሎ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ስለ ብርቱካን መፈታት በሚጠየቁበት ጊዜ በተደጋጋሚ የሚሰጡት መላሽ “የሕግ ጉዳይ ነው” የሚል ቢሆንም በቅርቡ በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ በተገኙበት ወቅት ሊቀመንበሯ ይቅርታ ከጠየቁ መንግስት ምህረት ሊያደርግ እንደሚችል ጠቁመው ነበር።

Read more

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ካቢኔያቸውን ሰየሙ

-ኀይለማርያም ደሳለኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኾኑ
-ሥዩም መስፍን እና ግርማ ብሩ ከካቢኔ ውጭ ኾነዋል
-በዛሬው የካቢኔ ሹም ሽር ከደሕዴግ እና ኦህዴድ አምስት፣ ከብአዴን አራት ፤ ከህወሓት እና ከሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶሕዴፓ) ሁለት ሚኒስትር ተሹመዋል። የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) አንድ ሚኒስትር አሹሟል። የፓርቲ አባል ያልኾኑት አቶ መኮንንም የሚኒስትርነት ሥልጣን ለመጀመርያ ጊዜ አግኝተዋል።

_ከተሿሚዎቹ መካካል ዐሥሩ አዲስ ናቸው

Read more